May 23, 2025 .
ስልጠና የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት የተቋማትን አፈጻጸም ከፍ ያደርጋል፡- ዶክተር ቀነኒሳ ለሚ (ተባባሪ ፕሮፌሰር)

ስልጠና የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት የተቋማትን አፈጻጸም ከፍ እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ዶክተር ቀነኒሳ ለሚ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) ተናገሩ፡፡
የምክር ቤቱ የማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች በሳይበር ደህንነት እና በስትራቴጂክ እቅድ ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል፡፡



በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይም መሰል ስልጠናዎች እና የአቅም ግንባታ ስራዎች የምክር ቤቱን የሪፎርም ተግባራት ለማሳካት የላቀ አስተዋጽ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡
ስልጠናውም በዘርፉ ላይ ያላቸውን እውቀት እና ክህሎት ከፍ እንደሚያደርገውም በስልጠናው የተሳተፉ ሰራተኞች ጠቁመዋል፡፡
መሰል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በሌሎችም መስከች እንደሚሰጡ ሲገለጽ ስልጠናውን ለሰጡት ባለሙያዎች እና ሰልጣኞችም የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡



